መጋቢት 12 በወገራ አምባጊዮርጊስ ከተማ ቀበሌ 02 እንዲሁም ወደ ገጠሩ ወጣ ብሎ ከምትገኘው ከምቢ ቀበሌ ልዩ ስሟ ተጎራ በሚባል መንደር የግዮን አባላት ተገኝተው ሶስት የተለያዩ የእርቅ ተግባሮችን ፈፅመዋል።“ደም በደም አይደርቅም”
Read Moreግዮን ዛሬ መጋቢት 8 በወገራ የእርቅ ገበታ ላይ ታድሞ ውሏል። በዛሬው የወረዳው ስምሪታችን በአምባጊዮርጊስ ከተማ በሚካኤል ቤተክርስቲያን የግዮን ሸምጋይ አባትና የደብሩ አስተዳዳሪ የሆኑት ቀሲስ ፈንታሁን ስለ ግዮን ፅኑ ዓላማና ስለ እርቅ ሳምንቱ አዋጅ ደብሩ ላይ ለተገኙ ምዕመናን ወምዕመናት ትልቅ እውቅናና የግንዛቤ ፈጠራ ስራ ሰርተዋል። በጥልና ክርክር ምክንያትነት ከሶስትነት ወደ ስድስትነት የተበተነው የወይበይ ልደታ ደብር የሰንበቴ […]
Read Moreበታች አርማጭሆ ወረዳ ሦሥት ቀበሌዎች ከህግ የራቁና በተለያየ ምክንያት የተጋጩ ግለሠቦችን ለማሥታረቅና ለማሥማማት አሥታራቂ ሽማግሌዎች ተቋቁመው የአካባቢው ህብረተሠብ ያጣውን ሠላም ወደነበረበት ለመመለሥ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ። ሽማግሌዎች የተቋቋሙት ከሀይማኖት አባቶች ፤ከአገር ሽማግሎች፤ከሤቶች እና ከወጣቶች ነው። ማንኛውም የአርማጭሆን ሠላም ፈላጊ በአካባቢው ም ያለ ከአካባቢው ውጭ የሆነ እና ከአገር ውጭ ያለም ቢሆን ከላይ የተዘረዘሩትን አሥታራቂ ሽማግሌዎች በፀሎት፤በሐሣብ እና […]
Read Moreግዮን የእርቀ ሰላምና ልማት ማህበር ሃገር በቀል የግጭት አፈታት መንገዶችን በመጠቀም ግጭቶችን የመለየት፤ የሃገር ሽማግሌዎችን ማደረራጀትና ግጭቶችን እንዲፈቱ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ባደረጋቸው ተግባራት በአምባ ጊዎርጊስና አካባቢው ማህበረሰብ ውስጥ ተፈጥረው የነበሩ ግጭቶችን መፍታት ተችሏል። በእነዚህ ግጭቶች ውስጥ ተሳትፎ የነበራቸው ከ10 በላይ የተጋጩ ሰዎች እርቅ ፈፅመው ወደ ሰላማዊ ኑሮ መመለሳቸውም ተገልጧል። “ደም በደም አይደርቅም”
Read Moreግዮን የእርቀ ሰላምና ልማት ማህበር “የእርቅ ሳምንት” በሚል የሁለት ወራት መርሃግብር በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ታች አርማጭሆ ወረዳ በሳንጃ ከተማ አስጀመረ። ይህ ፕሮግራም በበጎ ፈቃደኞች አማካኝነት የሚደረግ ሲሆን በአካባቢው ካለው የችግሩ ስፋት አኳያ በተመረጡ አካባቢዎች ለተከታታይ 2 ወራት የሚከናወን ነው። በመርሃ ግብሩ የሚከናወነውን የእርቅ ተግባር በተመለከተ፥ ዛሬ የካቲት 28 ቀን 2011 ዓ•ም በጎ ፈቃደኞች በማዕከላዊ ጎንደር […]
Read More