ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር ከዲኤክሲስ ኮንሰልቲንግ ግሩፕ ግምታቸው ከ180,000 ብር በላይ የሆነ የቢሮ ቁሳዊ ድጋፍ ተበረከተለት

ማኅበራችን ከዩስኤድ ጋር በመስራት የሚታወቀው ዲኤክሲስ ኮንሰልቲንግ ግሩፕ ግምታቸው ከ180,000 ብር በላይ የሚሆኑ የቢሮ ግብዓቶችን ለማኅበራችን አበርክቷል። ግብዓቶቹም ደረጃቸውን የጠበቁ ላፕቶፖች፣ ኮምፒዩተሮች፣ ፕሪንተርና ሌሎች ናቸው። የተበረከቱት ግብዓቶች ባለፉት ወራት በድርጅታቸው ኦቲአይ አጋርነት በሰራነው “ወጣቶችን ከሀይማኖት አባቶች ጋር የማገናኘት የውይይት ማዕቀፍ” በብቁ አተገባበራችን እንደሆነ በመጥቀስ ከበርካታ አጋር ሲቪክ ማኅበራት ጋር በንፃሬ የተሻለ የስራ አፈፃፀም በማስመዝገባችን እንደተበረከተልን […]

Read More

በመተባበር በሰላም አብሮ የመኖር ባህል ለማሳደግ የሚያስቾል የልምድ ልውውጥና የእርስ በርዕስ የመማማር አውደ ጥናት በጎንደር ከተማ ተካሄደ

ያለ መግባባት ችግሮችን በራስ አቅም ለመፍታት የሚያስችለውን ባህላዊ የሽምግልና የዳኝነት ስርዓት ማጠናከር ይገባል ተባለ። የወሎ ዩኒበርስቲ ፣ጊዎን የዕርቀ ሰላምና ልማት የበጎ አድራጎት ማህበር፣ፕሮ ዲቨሎፕመንት ኔት ወርክና ትራንዚሽን ኢኒሽቲቭ የተባለ የአሜሪካን ተራዶ ድርጅቶች በመተባበር በሰላም አብሮ የመኖር ባህል ለማሳደግ የሚያስቾል የልምድ ልውውጥና የእርስ በርዕስ የመማማር አውደ ጥናት በጎንደር ከተማ ተካሒዷል። በአውደ ጥናቱ ላይ የተገኙት የጊዎን ዕርቀ […]

Read More

ማኅበራችን መንገዘዝ ከተሰኘ የኪነጥበብ ድርጅት ጋር የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ 

አዲስ አበባ የሚገኘው መገዘዝ የኪነጥበብ ድርጅት በታዋቂው አርቲስት አንዱዓለም አባተ (የአፀደ ልጅ) የተመሰረተና የሚመራ ሲሆን በሰላም ዕሴት ግንባታና ግጭት መከላከል ላይ ያተኮረ ስራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች መክረናል። በኪነጥበብ መሣሪያነት የግጭት ቅድመ መከላከል ተግባራትን በተቀናጀ መንገድ ለመስራት የጋራ መግባቢያ ሰነድ (Memorandum of Understanding) ተፈራርመናል። ሰላማችሁ የበዛ ይሁን ግዮን ሰላምና ልማት ማህበር ታህሳስ፣ 2014 ዓ.ም

Read More

የማኅበራችን አባላትና ደጋፊዎች ደም ለገሱ

የማኅበራችን አባላትና ደጋፊዎች በጎንደር ከተማ ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ በመገኘት በዛሬው ዕለት ማለዳ 3:00 ጀምሮ የደም ልገሳ ፕሮግራም ማካሄድ ችለዋል። አባላቶቻችንና ደጋፊዎቻችን እናመሰግናለን። ሰላማችሁ የበዛ ይሁን ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) ሕዳር፣ 2014 ዓ.ም

Read More

ማኅበራችን “ወጣቶችን ከሀይማኖት መሪዎችና ከሸምጋይ አባቶች ጋር በማቀራርብ ሰላምን መገንባት” በሚል ርዕሰ ጉዳይ የአራት ቀናት የውይይት መድረክ አካሄደ

ማኅበራችን ከዩስኤድ ኦቲአይ ፕሮግራም ጋር በመተባበር በአይከል ከተማ እና በጎንደር ከተማ ዙሪያ ቀበሌዎች “ወጣቶችን ከሀይማኖት መሪዎችና ከሸምጋይ አባቶች ጋር በማቀራርብ ሰላምን መገንባት” በሚል ርዕስ የውይይት መድረክ አካሄደ። ይህ  የውይይት መድረክ ከጥቅምት 15-18/2014 ዓ/ም የተደረገ ሲሆን ከጎንደር ከተማና አይከል ከተሞች የተወጣጡ ወጣቶች፤የሃይማኖት ተቋማት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች በኤጂ ሆቴልና ሄርፋዚ ሪዞርት በአራት የመወያያ አዳራሾች በተለያዩ አጀንዳዎች ሲወያዩ […]

Read More

ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማኅበር ከዩስኤድ ኦቲአይ ፕሮግራም ጋር በመተባበር ወጣቶችን ከሀይማኖት መሪዎችና ከሸምጋይ አባቶች ጋር በማቀራርብ ሰላምን መገንባት በሚል የውይይት መድረክ አዘጋጀ

ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማኅበር ከዩስኤድ ኦቲአይ ፕሮግራም ጋር በመተባበር “በአይከል ከተማ እና በጎንደር ከተማ ዙሪያ ቀበሌዎች ወጣቶችን ከሀይማኖት መሪዎችና ከሸምጋይ አባቶች ጋር በማቀራርብ ሰላምን መገንባት በሚል የውይይት መድረክ” ለማዘጋጀት ከአመቻች ወጣቶች፣ ከሃይማኖት አባቶችና ሸምጋይ አባቶች ጋር ጥቅምት 12 እና 13 2014 ዓ/ም የምክክር መድረክ በጎንደር ከተማ ኤጂ ሆቴል ማካሄድ ችሏል። ከጎንደር ከተማና አይከል ከተማ […]

Read More

ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) በአይከልና ትክል ድንጋይ ከተሞች መድረኮች እንዲፈጠሩ ትልቅ ሚና ተጫወተ

የፌዴሬሽን ምክርቤት አፈ ጉባዔ አቶ አዳም ፈራዕና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ ሀላፊዎች በተገኙበት የሰላም መድረክ ማኅበራችን ግዮን ትልቅ ድርሻን ወስዷል። በተለይም የቅማንት ማኅበረሰብ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ የአሰላለፍ ውግንናው ከመላው ወንድም የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር መሆኑን በተግባር ያሳየበት ልዩ ታሪካዊ መድረክ እንደነበር ማስተዋል ተችሏል። ሰላማችሁ የበዛ ይሁን!! ግዮን ሰላምና ልማት ማህበር ነሀሴ፣2013 ዓ.ም

Read More

ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) ለአባሎቹ  የአቅም ግንባታ ስልጠና ስጠ

ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር በጎንደር ከተማ ስድስቱ ክ/ከተሞች ለተወጣጡ ከ60 በላይ ስመጥር አባቶች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ወጣቶችና እናቶች የአቅም ግንባታ ስልጠና በኦሎምፒክ ሆቴል   መስጠት ችሏል። ሰላማችሁ የበዛ ይሁን ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) ሐምሌ፣ 2013 ዓ.ም

Read More

በሽምግልና ምክንያት ልጃቸውን አፈር ማልበስ ያልቻሉት ርቱዕ አባት

እኒሁ አባት አደገ አመራ ይባላሉ። መኖሪያቸው ምዕራብ በለሳ አስዋጋሪ ቀበሌ ሲሆን ሙሉ ጊዜያቸውን ሽምግልና በተደገሰበት ዛፍ ፅላሎት ስር አይታጡም። አቶ አደገ ሽምግልናን በመጠቀም ብዙ የጥልና ክርክር ተቃርኖን በማስወገድ ዘለግ ያለ አበርክቶ አላቸው። በተለይ በጥቁር ደም (ደም መቃባት) ምድረ በለሴው ሲታወክ የተረበሸ ወገናቸውን ለመታደግ የሚቀድማቸው አልተገኘም። እንደሚታወቀው በለሳ ጀግንነቱ አርበኝነቱ የሚያጠያይቅ ባይሆንም በርስ በርስ መዳማቱ ላይ […]

Read More

የቀለጠፈ ዳኝነት በራያ ዘወልድ ሸምጋይነት

ራያ በህግ አምላክ ከምትለው ‘በዘወልድ አምላክ’ ብትለው ያነሳውን ይጥላል ለጠብ የተጋበዘበትን አጋጣሚ እርግፍ አድርጎ ይተዋል የሚባለው እሙን ነው። ከመደበኛው ፍርድ ቤት እጅግ በቀለጠፈና በተሻለ መንገድ ግጭቶችን የመፍታትም ሆነ ባለመብትነትን የማረጋገጥ ልዩ አቅም ያለው የራያ ቆቦው “የዘወልድ ሽምግልና”። ራያዎች በዕፁብ ተረካቸው አንድ ትዕውፊትን ያዘክራሉ። ሰንየ ሰገድ፣ ክፍሎ፣ መዘርድ እና ዘወልድ የሚባሉ አራት ወንድማማቾች ስም የሚጠራ የወንዝ […]

Read More