አፈ-ታረኩ እንደሚነግረን ከአንድ ሺህ ዓመት ዓለም ገደማ ከየመን ወደ ሀገር ቤት እንደገቡ የሚነገሩት ነገደ ዮቅጣን መሪያቸው ንጉስ ኢትዮጲስ ይባላል። ታዲያ ይህ ንጉስ ኢትዮጵያን አቅንቶ በስሙም አደላድሎ 55 ዓመታትን እንዳስተዳደረና አምስት ልጆችንም እንደወለደ የታሪክ መረጃዎች ይነግሩናል። ርስት ጉልት ያከፋፈላቸው አምስት ልጆቹም ሳባ ኖባ፣ በለው፣ ከለው፣ ላክንዱና ኖክ ይሰኛሉ። በመጀመሪያ ጠገዴን ለበለው አርማጭሆን ለከለው ርስት ሰጠ። ጠገዴን […]
Read Moreየመድረኩ በዙሪያ አጥቢያው የሚገኙ የአብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች፣ የክፍለ ከተማው አመራሮች፣ ከቀበሌውና ከአጎራባች ድባ ደፈጫ ግብዣ የተደረገላቸው የቀበሌ አመራሮች፣ የግዮን ሰላምና ልማት ማኅበር ሸምጋይ አባቶችና ወጣት አስተባባሪዎች፣ የአካባቢው የሁለቱ እምነት ተከታይ ነዋሪዎች ታድመዋል። የቀበሌው አስተዳዳሪ ጉባዔን መክፈቻ ሲያበስሩ መስጊዱ እንዲገነባ የአካባቢው ክርስቲያኖች ጉልህ ተዋፅዖን አስታውሰው ንግግራቸውን የጀመሩ ሲሆን የቀበሌው ሊቀመንበርና የመስጊዱ አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሴ […]
Read Moreግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) በጭልጋ ወረዳ አለምፀሀይ ቀበሌ አስተዳደር ጅባንሰግና አኩባይ ጎጦች ላይ ተፈናቅለው በአንከር አደዛ ቀበሌ ተጠልለው የሚገኙ ወገኖችን ከቀበሌው ማኅበረሰብ ጋር ተገናኝተው ወደነበሩበት ቀየ ለመመለስ የሚያስችል ምክክር ማካሄድ የቻለ ሲሆን በመድረኩም የማኅበሩ አባላት፣ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች የተገኙ ተገኝተዋል። በውይይቱም የተፈናቀሉት ወገኖችን ለመመለስ የመጠለያ ጉዳይ እንዲመቻች፤ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶች በዚሁ መንገድ ተጠናከረው […]
Read Moreግዮን ሰላምና ልማት ማኅበር ከዞብል ክ/ከተማ ጋር በመቀናጀት ጎንደሮች ጊዮርጊስ አካባቢ ተከታታይ የምክክር መድረኮችን አካሂዷል። ትላንት ግንቦት 28/2014 ዓ.ም የማኅበረሰብ አቀፍ ውይይቱም ሰላምን በዘላቂነት የሚያሰፍን እንደነበርና የመግባቢያ ነጥቦችን በማስቀመጥ ምክክሩን ማጠናቀቅ ተችሏል። የተፈናቀሉ ወገኖች ወደነበሩበት ሕይዎት እንዲመለሱ፣ ያልታረሱ መሬቶች ካሉ በፍጥነት እንዲታረሱ፣ የላሉ ማኅበራዊ ግንኙነቶች ወደነበሩበት እንዲመለሱ፣ ቂም በቀል የያዙ ተናጥላዊ ጉዳዮች በግዮን ሽማግሌዎች በዕርቅና […]
Read Moreበረዥም ዘመን ታሪክ እንዲሁም በገቢር ተፈትነው ከዳበሩ ስር የሰደደ ስርፀት ካላቸው ጎንደር አካባቢ ከሚከወኑ የሽምግልና ስነ-ስርዓትና ተግብሮት መሀል የአርማጭሆው “በአምስት” አንዱ ነው። *** ቃላዊ አስረጅዎች እንደሚያስረዱን አርማጭሆን ቀድመው ካቀኑ ነገስታት ቀዳሚው አፄ ናኦድ ናቸው። እኒሁ ንጉስ ታዲያ ከቀናት በአንዱ ከባድ የጥል ቋጠሮ ወደ ሸንጓቸው ሲቀርብ እንዲህ አሉ የሚል ትዕውፊታዊ የቃል ነገራ አለ። “እባካችሁ እነዚህን ጥለኞች […]
Read Moreበእርቅ ፕሮግራሙ የጊዮን አስታራቂ ማህበር እንዲሁም የዞብል ክፍለ ከተማ በሰላም አመካሪ እና የዞብል ክፍለ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፉ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ አስራደ ፣ የሀይማኖት አባቶች በተገኙበት ፕሮግራሙ ተካሂዷል። የአማራና የቅማንት ህዝባዊ አንድነቱን በማጠናከር የነበር አብሮነታችን በማሳደግ እና እንደጥንቱ የአባቶቻችን ዉበት እና ለዛ በማያዝ የነበር አብሮነታችን ለማስቀጠል የውሰጥ አንድነታች ለሀገራችን እና ለክልላችን ብሎም […]
Read Moreግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) ከሁለቱ የጎንደር ከተማ ገጠር ቀበሌዎች ማለትም ድባ ደፈጫና ፈንጠር እንዲሁም ከጎንደር ዙሪያ ወረዳ ከሚገኙ ስሆር ጉልቶችና ዳዋ ዳሞት ከተሰኙ ቀበሌ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ለሁሉም ቀበሌዎች አማካኝ በሆነችው ልዩ ስሟ “ስመ ክፉ” ትሰኝ ቦታ በመገናኘት ሰኔ 20/2014 ዓ.ም የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት በሚያሰፍን መንገድ ውይይትና የቀደመውን ግንኙነት ለመመለስ ያለመ ዝግጅት ተካሂዷል። […]
Read Moreበለሳ እና አካባቢዉን ከእርስ በርስ መዳማት ጋር በተያያዘ ያለውን ስም ለመፋቅና አካባቢዉን ከስጋት አርነት ለማውጣት ከተጉት መሀል የሙርሀንገብ ኪዳነ ምህረት ፍርድ ሸንጎዎች አንዱ ናቸው። በሙርሀንገብ ሸንጎ አያሌ የግጭት መዝገቦች ተዘግተዋል። ደም የተቃቡ በሽምግልና ቋንቋ ተግባብተው ደም አድርቀዋል። በዚህ የሙርሀንገብ ዳኝነት ወጥ የሆነና ሁሉም ማህበረሰብ ንቁ ሱታፌ ያደረገበት የማስቻያ አንቀፆች ተቀምጦላቸዋል። ለአብነት ምርሀንገቦች የጥቁርና ቀይ ደምን […]
Read Moreግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) አስተባባሪነት ግንቦት 14/2014 ዓ.ም በጎንደር ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች በአባ እንጢንዎስና በብላጅግ ድባርቃ ቀበሌ በመገኘት ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በሚያስገኙ አጀንዳዎች ዙሪያ በርካታ ሕዝብ በተገኘበት በጥልቅ ተመክሯል። የምክክሩ ዓብይ ጉዳይም ከአሁን በፊት በአማራና ቅማንት ወንድማማች ማኅበረሰቦች መካከል እኩያን ቀስቅሰውት በነበረው ግጭት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት የተዳረጉ ወገኖችን በማቀራረብ […]
Read Moreበግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) አስተባባሪነት ግንቦት 14/2014 ዓ.ም በላይ አርማጫሆ ወረዳ አስተዳደር ጎንደሮች ማርያም ቀበሌ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በሚያስገኙ አጀንዳዎች ዙሪያ በርካታ ሕዝብ በተገኘበት በጥልቅ ተመክሯል። የምክክሩ ዓብይ ጉዳይም ከአሁን በፊት በአማራና ቅማንት ወንድማማች ማኅበረሰቦች መካከል እኩያን ቀስቅሰውት በነበረው ግጭት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት የተዳረጉ ወገኖችን በማቀራረብ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በሚያስገኝ ጉዳይ […]
Read More