የጠገዴ ስምንቱ ማይቤት ባህላዊ የፍትህ ስርዓት-ሌላዉ ወርቃማ ዕሴታችን

አፈ-ታረኩ እንደሚነግረን ከአንድ ሺህ ዓመት ዓለም ገደማ ከየመን ወደ ሀገር ቤት እንደገቡ የሚነገሩት ነገደ ዮቅጣን መሪያቸው ንጉስ ኢትዮጲስ ይባላል። ታዲያ ይህ ንጉስ ኢትዮጵያን አቅንቶ በስሙም አደላድሎ 55 ዓመታትን እንዳስተዳደረና አምስት ልጆችንም እንደወለደ የታሪክ መረጃዎች ይነግሩናል። ርስት ጉልት ያከፋፈላቸው አምስት ልጆቹም ሳባ ኖባ፣ በለው፣ ከለው፣ ላክንዱና ኖክ ይሰኛሉ። በመጀመሪያ ጠገዴን ለበለው አርማጭሆን ለከለው ርስት ሰጠ። ጠገዴን […]

Read More

በፋሲል ክ/ከተማ ሳይና ሳቢያ ቀበሌ ሸምበቂት በተሰኘች ትንሽየ ከተማ የሙስሊም ክርስቲያኑን የአብሮነት ታሪካዊ ኑባሬ የሚያስቀጥል ምክክር መድረክ ተዘጋጀ

የመድረኩ በዙሪያ አጥቢያው የሚገኙ የአብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች፣ የክፍለ ከተማው አመራሮች፣ ከቀበሌውና ከአጎራባች ድባ ደፈጫ ግብዣ የተደረገላቸው የቀበሌ አመራሮች፣ የግዮን ሰላምና ልማት ማኅበር ሸምጋይ አባቶችና ወጣት አስተባባሪዎች፣ የአካባቢው የሁለቱ እምነት ተከታይ ነዋሪዎች ታድመዋል። የቀበሌው አስተዳዳሪ ጉባዔን መክፈቻ ሲያበስሩ መስጊዱ እንዲገነባ የአካባቢው ክርስቲያኖች ጉልህ ተዋፅዖን አስታውሰው ንግግራቸውን የጀመሩ ሲሆን የቀበሌው ሊቀመንበርና የመስጊዱ አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሴ […]

Read More

በጭልጋ ወረዳ አለምፀሀይ ቀበሌ ጅባንሰግና አኩባይ ጎጦች ላይ ተፈናቅለው በአንከር አደዛ ቀበሌ ተጠልለው የሚገኙ ወገኖችን ለመመለስ የሚያስችል ምክክር ተካሄደ

ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) በጭልጋ ወረዳ አለምፀሀይ ቀበሌ አስተዳደር ጅባንሰግና አኩባይ ጎጦች ላይ ተፈናቅለው በአንከር አደዛ ቀበሌ ተጠልለው የሚገኙ ወገኖችን ከቀበሌው ማኅበረሰብ ጋር ተገናኝተው ወደነበሩበት ቀየ ለመመለስ የሚያስችል ምክክር ማካሄድ የቻለ ሲሆን በመድረኩም የማኅበሩ አባላት፣ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች የተገኙ ተገኝተዋል። በውይይቱም የተፈናቀሉት ወገኖችን ለመመለስ የመጠለያ ጉዳይ እንዲመቻች፤ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶች በዚሁ መንገድ ተጠናከረው […]

Read More

አብሮነትና መቻቻልን ማጠናከር የሚያስችል የምክክር መድረክ በጎንደሮች ጊዮርጊስ ተካሄደ

ግዮን ሰላምና ልማት ማኅበር ከዞብል ክ/ከተማ ጋር በመቀናጀት ጎንደሮች ጊዮርጊስ አካባቢ ተከታታይ የምክክር መድረኮችን አካሂዷል። ትላንት ግንቦት 28/2014 ዓ.ም የማኅበረሰብ አቀፍ ውይይቱም ሰላምን በዘላቂነት የሚያሰፍን እንደነበርና የመግባቢያ ነጥቦችን በማስቀመጥ ምክክሩን ማጠናቀቅ ተችሏል። የተፈናቀሉ ወገኖች ወደነበሩበት ሕይዎት እንዲመለሱ፣ ያልታረሱ መሬቶች ካሉ በፍጥነት እንዲታረሱ፣ የላሉ ማኅበራዊ ግንኙነቶች ወደነበሩበት እንዲመለሱ፣ ቂም በቀል የያዙ ተናጥላዊ ጉዳዮች በግዮን ሽማግሌዎች በዕርቅና […]

Read More

የአርማጭሆ አምስት(የደም በቃ ዛፍ ስር ፍትህ)!

በረዥም ዘመን ታሪክ እንዲሁም በገቢር ተፈትነው ከዳበሩ ስር የሰደደ ስርፀት ካላቸው ጎንደር አካባቢ ከሚከወኑ የሽምግልና ስነ-ስርዓትና ተግብሮት መሀል የአርማጭሆው “በአምስት” አንዱ ነው። *** ቃላዊ አስረጅዎች እንደሚያስረዱን አርማጭሆን ቀድመው ካቀኑ ነገስታት ቀዳሚው አፄ ናኦድ ናቸው። እኒሁ ንጉስ ታዲያ ከቀናት በአንዱ ከባድ የጥል ቋጠሮ ወደ ሸንጓቸው ሲቀርብ እንዲህ አሉ የሚል ትዕውፊታዊ የቃል ነገራ አለ። “እባካችሁ እነዚህን ጥለኞች […]

Read More

በጎንደር ዞብል ክፍለ ከተማ በአባ እንጦኒዎስ ቀበሌ የአማራ ማኅበረሰብ እና የቅማንት ማህበረሰብ ላይ የተፈናቀሉ ማህበረሰቦችን ወደ መኖሪያ ቀያቸው የመመለስና የእርቅ መርሃ ግብረ ተካሄደ

በእርቅ ፕሮግራሙ የጊዮን አስታራቂ ማህበር እንዲሁም የዞብል ክፍለ ከተማ በሰላም አመካሪ እና የዞብል ክፍለ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፉ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ አስራደ ፣ የሀይማኖት አባቶች በተገኙበት ፕሮግራሙ ተካሂዷል። የአማራና የቅማንት ህዝባዊ አንድነቱን በማጠናከር የነበር አብሮነታችን በማሳደግ እና እንደጥንቱ የአባቶቻችን ዉበት እና ለዛ በማያዝ የነበር አብሮነታችን ለማስቀጠል የውሰጥ አንድነታች ለሀገራችን እና ለክልላችን ብሎም […]

Read More

የነበሩ ማኅበራዊ ግንኙነቶችን ወደ ቀደመ ኑባሬያቸው እንዲመለሱ ያለመ ዝግጅት በአራት ቀበሌ ሕዝቦች መካከል ተደረገ

ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) ከሁለቱ የጎንደር ከተማ ገጠር ቀበሌዎች ማለትም ድባ ደፈጫና ፈንጠር እንዲሁም ከጎንደር ዙሪያ ወረዳ ከሚገኙ ስሆር ጉልቶችና ዳዋ ዳሞት ከተሰኙ ቀበሌ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ለሁሉም ቀበሌዎች አማካኝ በሆነችው ልዩ ስሟ “ስመ ክፉ” ትሰኝ ቦታ በመገናኘት ሰኔ 20/2014 ዓ.ም የአካባቢውን ሰላም በዘላቂነት በሚያሰፍን መንገድ ውይይትና የቀደመውን ግንኙነት ለመመለስ ያለመ ዝግጅት ተካሂዷል። […]

Read More

የሙርሀንገብ ዳኝነት እና በለሳ—ነባር ይትባህሉ ወደ ፊት ሊመጣ የሚገባዉ ስርዓት

በለሳ እና አካባቢዉን ከእርስ በርስ መዳማት ጋር በተያያዘ ያለውን ስም ለመፋቅና አካባቢዉን ከስጋት አርነት ለማውጣት ከተጉት መሀል የሙርሀንገብ ኪዳነ ምህረት ፍርድ ሸንጎዎች አንዱ ናቸው። በሙርሀንገብ ሸንጎ አያሌ የግጭት መዝገቦች ተዘግተዋል። ደም የተቃቡ በሽምግልና ቋንቋ ተግባብተው ደም አድርቀዋል። በዚህ የሙርሀንገብ ዳኝነት ወጥ የሆነና ሁሉም ማህበረሰብ ንቁ ሱታፌ ያደረገበት የማስቻያ አንቀፆች ተቀምጦላቸዋል። ለአብነት ምርሀንገቦች የጥቁርና ቀይ ደምን […]

Read More

ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) በሁለት የጎንደር የገጠር ቀበሌዎች በመገኘት ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በሚያስገኙ አጀንዳዎች ዙሪያ ማኀበረሰብ አቀፍ ውይይት አካሄደ

ግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) አስተባባሪነት ግንቦት 14/2014 ዓ.ም በጎንደር ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች በአባ እንጢንዎስና በብላጅግ ድባርቃ ቀበሌ በመገኘት ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በሚያስገኙ አጀንዳዎች ዙሪያ በርካታ ሕዝብ በተገኘበት በጥልቅ ተመክሯል። የምክክሩ ዓብይ ጉዳይም ከአሁን በፊት በአማራና ቅማንት ወንድማማች ማኅበረሰቦች መካከል እኩያን ቀስቅሰውት በነበረው ግጭት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት የተዳረጉ ወገኖችን በማቀራረብ […]

Read More

ማህበሩ በላይ አርማጫሆ ወረዳ ጎንደሮች ማርያም ቀበሌ በመገኘት ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በሚያስገኙ አጀንዳዎች ዙሪያ ማኀበረሰብ አቀፍ ውይይት አካሄደ

በግዮን የዕርቀ ሰላምና ልማት ማህበር (ግዕሰልማ) አስተባባሪነት ግንቦት 14/2014 ዓ.ም በላይ አርማጫሆ ወረዳ አስተዳደር ጎንደሮች ማርያም ቀበሌ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በሚያስገኙ አጀንዳዎች ዙሪያ በርካታ ሕዝብ በተገኘበት በጥልቅ ተመክሯል። የምክክሩ ዓብይ ጉዳይም ከአሁን በፊት በአማራና ቅማንት ወንድማማች ማኅበረሰቦች መካከል እኩያን ቀስቅሰውት በነበረው ግጭት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት የተዳረጉ ወገኖችን በማቀራረብ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በሚያስገኝ ጉዳይ […]

Read More